አዲስ አመት እና ሌሎች በአላትን ማህበሩ ከኢትዮጵያውያን እና ሌሎች ፍላጎት ካላቸው ዜጎች ጋር ያከብራል። እነዚህ በዓላት ሲከበሩ ልክ እንደ ኢትዮጵያ በዕለቱ ቀን ባይሆንም ቀራቢው ቅዳሜ ላይ ይከበራሉ። ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች በአላትን አብረው ሲያከብሩ ማህበሩን ለማወቅ አንዱ ጥሩ አጋጣሚ ነው፡፡ ቤተሰቦች፣ ግለሰቦችና የሀይማኖት ተቋማት በዕለቱ ላይ እንደሚያከብሩ ይታወቃል፡፡
ለነዚህ በዓላት ዝግጅቶች ማህበሩ ቅድሚያ እንዳለው ይታወቃል፡፡ ለብዙ አመታት ሲሰራበትም ቆይቷል፡፡ ከማህበሩ ውጭ በተመሳሳይ ቀን ላይ ዝግጅት የሚያደርጉ አካላት ቀደም ብለው ማህበሩን ቢያሳውቁት መልካም ነው፡፡ ድርብ ዝግጅቶች እንዳይኖሩ ማህበሩ ከሌሎች አካላት ጋር በጋራ መፍትሄ ለማግኘት ይጥራል፡፡ ማህበሩ ቀራቢው ቅዳሜ ላይ ለማክበር የወሰነበት ምክንያት ውጭ ስለምኖር ከስራም ወይም ከትምህርት አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ነጻ የሚሆንበት ቀን ቅዳሜ ስለሆነ ነው፡፡
እነዚህ በዓላት በሰፊውና ባዝናኝ መልኩ ምቹ ሆነው እንዲከበሩ ማህበሩ የተቻለውን ሁሉ ያደርጋል፡፡ ቀን ላይ የልጆችና የቤተሰቦች ዝግጅት አለ፡፡ አንዳንዶቹ እንቅስቃሴዎች የልጆች ጨዋታ፣ ውድድር፣ ሽልማት፣ የልጆች ዘፈን፣ ምግብና መጠጦች፣ የቡና ስናስርዕት የመሳሰሉት ናቸው፡፡ ምሽት ላይ ደግሞ ከምግብና ከመጠጥ ጋር የሙዚቃ ምሽት አለ፡፡
ከታች አስተያየት ወይም ነጥብ ይስጡ!
Error: No site found with the domain 'mail.ethionorway.org' (Learn more)